Breaking News
Home / Amharic / የዘር ጭፍጨፋ በኢትዮጵያ። መነበብ ያለበት!

የዘር ጭፍጨፋ በኢትዮጵያ። መነበብ ያለበት!

የዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈፀመ

በኢትዮጵያ የዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈፅሞዋል የአገሪቱ መንግስት በተባበሩት መንግስታት ሰብአዊ መብት የፀጥታው ምክር ቤት ሳይቀር ከፍተኛ ጫና ተነስቶበታል።

ንፁሀንን ቆመው አስገድለዋል እራሳቸውን እንኩዋን እንዳይከላከሉ በክልሉ የፀጥታ ሀይሎች ጭምር ግድያ ተፈፅሞዋል ። ንፁሀን ቤታቸው ውስጥ ተቃጥለዋል የማምለጫ በሮች በክልሉ ልዩ ሀይል ዝግ ተደርጎባቸው በቀጥታ በአሰቃቂ ሁኔታ ብዙወች ተገድለዋል በዚህም የዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈፅሞዋል ሲልም የነገሩን ጉዳይ አክፍቶታል።

አለማቀፉ ሲፒጄ በበኩሉ የክልሉ የፀጥታ አካላት ቆመው እያሳለፉ ቄሮ በተባለው ቡድን እና ሌሎች በታጠቁ አካላት በቀጥታ በማስገባት ከሰው ዘር የማይጠበቅ ወንጀል ተሰርቶዋል በዚህም አለማቀፍ ገለልተኛ አጣሪ ገብቶ ወንጀሉን ኢንቨስቲጌት ያደርግ ዘንድ ጥሪ አቅርቦዋል።

በኦሮምያ ክልል የተደረገው የዘር ጭፍጨፋ ሆን ተብሎ የታቀደበት ይመስላል የክልሉ የፁጥታ አካላት ቆመው ከማየት እስከ ማገዝ የደረሱ አሳዛኝ ወንጀል ፈፅመዋል ንፁሀን ዜጎችን በየቤታቸው ገብተው ሲገሉ ፈቅዶ ተባባሪ ነበር ሲልም ከሱዋል።

ይህ ብቻ ግን አይደለም በክልሉ የተፈፀመው ወንጀል በገለልተኛ አጣሪ ኮሚሽን ከመታየት አልፎ በአለማቀፍ የዘር ማጥፋት ወንጀል በህግ መዳኘትም አለበት ሲል አሳስቦዋል ይህ ወንጀል አሳዛኝም ክስተት ነው ሲልም አስምሮበታል።

ህፃናትን ደፍረው በስለት ቆራርጠዋል ፣ እናቶች አንገታቸው ተቆርጦዋል ፣ ቤት ተዘግቶባቸው ከነቤታቸው ብዙወች ነደዋል፣ የክልሉ የፀጥታ አካላት ጭምር ንፁሀንን በጥይት ገድለዋል ፣ የተደራጁ ስለት መሳሪያ ገጀራ የያዙ ገብተው እንዲገድሉ ድጋፍ ተሰቶዋቸዋል ከሚል አንስቶ የሰወች አካልት ተቆራርጦ መንገድ ላይ ተጎትቶዋልም ሲል አትቶዋል።

አለማቀፉ የሰብአዊ መብት ድርጅት ጂኖሳይድ ተፈፅሞዋል እጅግም አስከፊ ነው ሲልም አሳዛኙን ዘገባ በቅርብ ለአለም ይፋ እንደሚያደርግ ጠቁሞዋል።

እስካሁን ከ190 በላይ ንፁሀን እንደተገደሉ ቢዘገብም ይህ ቁጥር ከ800 እንደሚልቅ እየጠቆሙ ያሉ አሉ።

የአገሪቱ መንግስት የንፁሀን ዜጎቹን ህይወት መታደግ ያልቻለም በሚል ክስ ቀርቦበታል።

የአውሮፓ ህብረት በበኩሉ የዘር ማጥፋት ወንጀል መፈፀሙ ሪፖርት ደርሶናል ሲሉ የኮሚሽኑ ፀሀፊ ቃል ሰተዋል።

በዝዋይ ፣ሀረር፣ ሻሸመኔ፣ ናዝሬት በመሳሰሉት የተፈፀመው ግፍ የከፋ ነው ።

በሻሸመኔ ለረዥም ጊዜ በሰላም ይኖሩ የነበሩ ጃማይካውያን ሳይቀር እንደተገደሉ ንብረታቸው እንደወደመም ተገልፆዋል።

የዘር ማጥፋት ወንጀል ከተፈፀመባቸው ንፁሀን ከ85% በላዩ አማራ ኢትዮጵያውያን እንደሆኑ መረጃወች ይጠቁማሉ።

የአገሪቱ ኢንተርኔት መዘጋትን ተከትሎ ኢንተርኔት ሲለቀቅ የሚወጡ አሳዛኝ ቪዲዮወች እና ፎቶወች የአገሪቱን ህዝብ አይምሮ በጣም የሚዘገንኑ እና የሚረብሹ ሊሆኑ ስለሚችሉ ካሁኑ ለዚህ የስነ ልቦና ዝግጅት ያደርግ ዘንድ ብዙወች በማሳሰብ ላይ ናቸው ።

በአዲስ አበባ የተደረገውን ክስተት የአገሪቱ መንግስት የዋና ከተማዋን ማስጠበቅ ሳይችል ከከተማዋ ነዋሪ ውጭ ገብተው የከተማዋን ነዋሪወች ሲገደሉ ዝም ብሎ ያየ በሚል ከባድ ጥያቄም እየተነሱ ነው ።ከተማዋ የራሱዋ የፀጥታ አካል የከተማዋን ህዝብ የሚያድን ባለመኖሩ በአምስቱም በሮቹዋ መሳሪያ የታጠቁ ዱላ እና ስለት የያዙ ገብተው ሰላማዊ ህዝቡን ገድለዋል ንብረት አውድመዋል ይህ እንዲሆን የፈቀደው የመንግስት ትልቅ ስህተት ነው በሚል በከተማዋ የሚገኙ አለማቀፍ ድርጅቶች ቁጣቸውን አሰምተዋል። ከዚህም ባለፈ የአፍሪካ ህብረት በተደጋጋሚ ከተማዋ ሰላም የሚነሱዋት እየገቡ የህብረቱ ደህንነት ስጋት ውስጥ እንደገባ ተሰምቱዋል የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበርም በአጭር መልክት ከፍተኛ ስጋታቸውን ገልፀዋል። ከዚህም ባለፈ እንዴት የአገሪቱ መንግስት የብዙ አለማቀድ ድርጅቶች መቀመጫን በተደጋጋሚ ሆ ብለው እየገቡ ወንጀል ለሚፈፅሙ ፈቀደ የሚለው ጉዳይ በተደጋጋሚ ጊዜ በመሆኑ መሰላቸቶች እየታዩ መሆኑንም ተመልክቶዋል። ምናልባትም በቀጣይ እንዲህ አይነት ክስተቶች ከቀጠሉ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫውን ወደሌላ ሰላማዊ የአፍሪካ አገራት ሊያደርግ እንደሚችል ፍንጭ ሰቶ ነበር ። ይህ ከቀጠለ ለህብረቱ መቀመጫ ደቡብ አፍሪካ ፣ግብፅ እና ናይጀሪያ ከሶስቱ አንዳቸው ላይ ሊሆን እንደሚል ከዚህ ቀደም ሀሳብ ተሰቶ ነበር ።

በመጨረሻም ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የስነ ልቦና ዝግጅት ያደርግ ዘንድ እኔም ጥሪየን አቀርባለሁ ። የዘር ማጥፋት ወንጀሉ በቪዲዮም በምስልም በብዛት ሊወጣ ስለሚችል እጅግ ሰቅጣጭ የሆነ ከሰው ዘር የማይጠበቁ ወንጀሎች ሊታዩ ስለሚችሉ ካሁኑ ይጠነቀቅ ዘንድ እመክራለሁ ።

ሰላም

@ልጅ አቤል

Check Also

በአሜሪካን ሀገር የምትኖሩ የአማራ ማህበራትና የአማራ ልጆች የት ነው ያላችሁት?? Share!

ድሮን ሲያስተኩስ የነበረው ባንዳ በፋኖ ተያዘ ! እኔን ያየህ ተቀጣ !

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.