Breaking News
Home / Amharic / የአብን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ክርስቲያን ታደለና የአብን አባላት ታሰሩ!

የአብን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ክርስቲያን ታደለና የአብን አባላት ታሰሩ!

በጥሞና አንብቡልኝ
ሶሻል ሚዲያን በመዝጋት በመንግስት በሚተዳደሩ ሚዲያዎች ነገሮችን በመደጋገም የእውሸት ቅንብርን እውነት ለማስመሰል እየተሞከረ ይገኛል ።
1/ የጄኔራል ሳእረን ገዳይ አንዴ ጠፍቶል ፣ አንዴ እራሱን ገድሏል ፣ አንዴ ታርጋ የተለጠፈለት ልጂ ገዳዮ ቆስሏ ሆ/ል ገብቶል ብለው ቆመሩ..
2/ የክልሉ አመራሮች ተገድለዋል እንደተገደሉም በ 20 ደቂቃ ውስጥ ሳይጣራ መፈንቅለ መንግስት ነው ብለው እራሳቸው አወጁ..ከምኔው ተጣርቶ መፈንቅለ መንግስት ተባለ?
3/መፈንቅለ መንግስት ሲታሰብ መፈንቅለ መንግስት አድራጊው ሀይል ሚዲያውን እና ትልልቅ ተቋማትን ይቆጣጠር ነበር በተቃራኒው ግን ከመፈንቀለ መንግስቱ በፊት የመከላከያ ሀይሉ መገናኛ ብዙሀኑን እና ምክርቤቱን ከበውት ነበር…
4/ጠ/ሚ/ሩ ምሽት ላይ መግለጫ ሲሰጡ የአማራ ቲቪ ማይክ ብቻ ነበር ፊት ለፊቱ ላይ የነበር እናም በወቅቱ ጠ/ሚ/ሩ ባህር ዳር ነበሩ ማለት ነው?
5/ጀኔራል አሳምነው ከወራት በፊት ባደረጉት ንግግር እኛ ያላወቅነው የፌደራል ልኡክ በ 3 አቅጣጫ ወደ አማራ ክልል እንደገባ ተናግረው ነበር..
6/ ጀኔራል አሳምነው ከሳምንት በፊት ልዮ ሀይል ሲያስመርቁ የአማራ ክልል ተከቧል ብለውም ነበር..
7/ በወቅቱ አቶ ምግባሩ ቆስሎ ሆስፒታል ይዘውት የመጡት ልዮ ሀይሎች ገዳዮቹ ወዘ ልውጦች/ እኛ የማናውቃቸው/ ናቸው ሲሉም ተደምጠው ነበር..
8/ በወቅቱ ተኩስ እና ግርገር የተጀመረው ከምክር ቤት በፊት ፓሊስ ኮሚሽን ላይ ነበር ስለሆነም ጄ/ል አሳምነውን ለማፈን ኦፕሬሽን ነበር አሳምነውም ከእነ አምባቸው በፊት ተሰውቷል ማለት ነበር…
9/የኦሮምያ ር/መ/ር መግለጫ ሲሰጡ ከዚህ በሆላ አንታገስም አሉ…የቤኒሻንጉል ጉምዝ ከፍተኛ አመራሮች ሲገደሉ አንታገስም አላሉም…ኦነግ 17 ባንክ ሲዘርፍ አንታገስም አላሉም..ብራዮ ላይ ኦነግ በመቶ የሚቆጠሩ ሰወችን አንገት ሲቆርጥ አንታገስም አላሉም…ዛሬ ግን ያለውን ሰምታቹሀል ።።
ጠቅለል ሲል የኢፌዲሪ መከላከያ ሀይል ከላይ እስከ ታች በአንድ ቢሄር ተጠቅጥቆል ጄ/ል ሰአረ ስራ መስራት ከማይችልበት ደረጃም ደርሶ ነበር አሁንም በአቶ ሳአረ ቦታ ሊተኩት ያሰቡት አቶ ብርሃነ የኦሮሞን አንድነት እመልሳለሁ ብሎ ከተለያዮ የኦሮሞ ኮንፈረንሶች ሲታይ የነበረው ሰውን ነው…
አራት የአማራ ከፍተኛ አማራሮች እና የእነ ጄ/ል ሳእረን ሞት በንቃት እና በብልጠት ልንከታተለው ይገባል። አላማውም የአማራን ጠንካራ ወጣት በሰበብ በማሰር የአማራን ልዮ ሀይል በማፍረስ ክልሉን በፌደራል መከላከያ ሀይል መምራት ነውና ።
21/10/11

ፍትህን ከመጠየቃቺን በፊት ፍትህን ከማን ነው የምንጠይቀው የሚለውን እናስብ ፍትህን ከነሳ ፍትህ አይጠየቅም ሰላምን ከነሳ ሰላም ስጠኝ አይባልም ነፆነትን ከነጠቀ ነፆነት ኡይጠየቅም ይልቁንስ በመላው አለም ያለህ አማራ ተነስ ለህዝብህ ፍትህ ጠይቅ ለአለም አሳወቅ አማራነት ወንጄል ሆኖባቸው ለታሰሩ ወገኖችህ እርስ በእርስ ከምትዘላለፍ አገር ቤት መሬት የወረደ ስራ ሰርተን መሬት አንቀጥቅጥ ሰልፍ እንጥራ 
በተረፈ ዝም ብሎ ማላዘን ዋጋ የለወም::

 

Check Also

AMHARA FANO in London at Ethiopian Embassy

የዲያስፓራ መንገደኞች የሚያጋጥማቸው መከራ!

በቦሌ አየር ማረፊያ በፍተሻ እና ጥበቃ አካላት ተጓዦች ላይ የሚፈፀም ውንብድና እና ዝርፊያ! ድርጊቱ የተፈፀመው …

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.