Breaking News
Home / Amharic / የአማራ ማህበር በካናዳ ለሰብአዊ መብት ትላንት August 4, 2019 ዓ ም በቶሮንቶ ከተማ ያደረገው ስብሰባ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።

የአማራ ማህበር በካናዳ ለሰብአዊ መብት ትላንት August 4, 2019 ዓ ም በቶሮንቶ ከተማ ያደረገው ስብሰባ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።

የአማራ ማህበር በካናዳ ለሰብአዊ መብት
ትላንት እሁድ August 4, 2019 ዓ ም
በቶሮንቶ ከተማ ያደረገው ስብሰባ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።

የስብሰባው ዋና አላማ በአማራ ሕዝብ ወቅታዊ ሁኔታ ለመወያየትና አማራው ወገናችን ራሱን ለመከላከል በሚያደርገው ትግል ፤ በአለም ዙሪያ የምንገኝ ስደተኛ አማራዎች እገዛ ለማድረግ በምን መስመር መሰለፍ ይኖርብናል የሚለውን አቅጣጫ በማመልከት፥
አማራ ሕዝብ የተቃጣበት የህልውና አደጋ ስርዓተ-መንግሥታዊ መሆኑን በማስገንዘብ ጠላቶቹ በተነሱበት መጠን ለመመከት በፖለቲካ ብቻ ሳይሆን አማራ ነኝ ብሎ በሙያና በመረዳጃ ማህበር ተደራጅቶ መታገል እንዳለበት ግንዛቤ ለማስጨበጥ ያለመ ሲሆን፥
የአማራ ማህበር በካናዳ የዐአማራ ድርጅቶችና ማህበራት ስብስብ ዐድማስ አካል በመሆን የጀመረውን የተቀናጀ ስራና አሥራት ሚዲያን ለህዝብ በማስተዋወቅ፤
በሚዲያና በዲፕሎማሲ ለተጀመረው ትግል አስፈላጊውን አስተዋጽኦ ለማድረግ እንድንችል ማህበራችን በአባላትና በአመራር አጠናክረን መገኘት የታቀዱ ስራዎችን ለመደገፍ ብቃት ይሰጠናል የሚለውን ሁሉ ያካተተ፥
ፕሮፌሰር ሐብታሙ ተገኝ እና አቶ ሆነ ማንደፍሮ የተገኙበት ከቶሮንቶ እና አካባቢ ከተማዎች የመጡ በርከት ያሉ አማራዎች የተሳተፉበት ሰፊ ውይይትና፤ አማራ ሕዝብ ቆርጦ መነሳቱን ያየንበት ሰፊ ውይይት ተደርጎ ስብሰባው ተጠናቋል።

አንድ አማራ ለሁሉ አማራ፤ ሁሉ አማራ ለአንድ አማራ!

Check Also

ድሮን ሲያስተኩስ የነበረው ባንዳ በፋኖ ተያዘ ! እኔን ያየህ ተቀጣ !

ከጎጃም አማራ ፋኖ የተሰጠ መግለጫ – ዘመነ ካሴ – Amhara FANO Gojjam

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.