Angaw Mulu
ህውኃት መቀሌ የሚገኘውን አውሮፕላን ማረፊያ አሉላ አባ ነጋ፣ አክሱም የሚገኘው አጼ ዮሀንስ 4ኛ ብሎ ሰይሞ ወደ አማራይቱ መዲና ባህር ዳር ግን ስንመጣ ደግሞ ግንቦት 20 አለማቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ብሎ ሰይሞታል።
ሌላው ቢቀር ጅማ ስንሄድ አባ ጅፋር ኤርፖርት ነው ሚባለው። ጎንደርም ስንሄድ በአጼ ቴወድሮስ ስም ነው የተሰየመው።
በባህር ዳር ወይም በአማራ ህዝብ ምን የተለየ ነገር ኖሮ ነው በጀግናችን በበላይ ዘለቀ ስም እንዳይሰየም የተደረገው? ዛሬም ድረስ የህውኃት ሎሌ ሆኖ የኖረው ብአዴን/አዴፓ ከላይ በወረደ ትዕዛዝ ከህዝብ ፍላጎት ውጭ በሀገር ባለውለታው ጀግና በላይ ዘለቀ ስም እንዲሰየም ማድረግ አልቻለም። አቅምም ማግኘት አልቻለም።
አሁንም ከላይ ያሉ አካላት ይህንን ጉዳይ ትኩረት ሰጥተው እንዲያስቡበት እና ከግንቦት 20 ወደ በላይ ዘለቀ አውሮፕላን ማረፊያ እንዲቀየር እንጠይቃለን።
ግንቦት 20ን ከፈለገ መቀሌ ወይም አክሱም ለዘላለም ይውሰደው።
አዴፓ ግዴታ እንዲቀየር ማድረግ አለበት! #ሼር
ዉዱ አማራ ነኝ ከቆልቆሌ ጋራ