Breaking News
Home / Amharic / ወልቃይት_ጠገዴ_ጠለምትና_ራያ በታሪክ የአማራ ሕዝብ አፅመ ርስቶች ናቸው።

ወልቃይት_ጠገዴ_ጠለምትና_ራያ በታሪክ የአማራ ሕዝብ አፅመ ርስቶች ናቸው።

#ወልቃይት_ጠገዴ_ጠለምትና_ራያ በታሪክ የአማራ ሕዝብ አፅመ ርስቶች ናቸው።

በህገመንግስቱም ቢሆን ቅቡልነት የለውም።
-ወልቃይት ከጎንደር ተቆርሶ ወደ ምዕራብ ትግራይ፣
-ራያ ከወሎ ተቆርሶ ወደ ደቡብ ትግራይ
-መተከል ከጎጃም ተቆርሶ ወደ ቤንሻንጉል
:
የተካለሉት አማራ ያልተወከለበት ህገመንግስት ተብየው
ከመጽደቁ በፊት በ1984 ዓ.ም. ሲሆን ህገመንግሥቱ የጸደቀው ደግሞ ከሦስት ዓመት በኋላ በ1987 ዓ.ም. ነው።
ስለዚህ ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምትና ራያ በትህነግ በሀይል ተወሰዱ፥ አሁን ደግሞ የአማራ ልዩ ሀይል፣ ሚሊሻና ፋኖ ክቡር መስዋዕትነት ከፍሎ በጀግንነት ነጻ አወጣቸው።

እናም የአማራ ልዩ ሀይልና ሚሊሻ መስዋዕትነት ከፍሎ ነጻ ያወጣቸውን ግዛቶቹን መልሶ በትግራይ ክልል አስተዳደር የሚሰጥበት ታሪካዊ ሆነ ህገመንግስታዊ ምክንያት የለም።

ይህን ቀይ መስመር ማለፍ አይቻልም!!

  • በትግራይ ክልል የሚቋቋመው ጊዚያዊ መንግሥት ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሙሉ ነጋ፦
    << የወልቃይትም ሆነ የራያ መሬቶች የብአዴን ባለስልጣናት ትናንት ፈቅደው ወደ ትግራይ እንዲካለል አድርገዋል፤ ዛሬም ሐገራዊ ለውጡን ተከትሎ #በጣት_የሚቆጠሩ ‘የወልቃት ተወላጆች’ የማንነት ጥያቄ ቢያነሱም ህጉን ተከትለን #በትግራይ #ክልል #የአማራ #ብሔረሰብ #ልዩ #ዞን #በወልቃይት #ይመሰረታል” ብሏል የተባለውን ለማጣራት ሞክሬያለሁ፤ እዚህ የተፃፈው ቃል በቃል ባይሆንም #ሀሳቡ #ትክክል ነው [የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ጦርነቱ የእርስት ማስመለስ አይድለም የሚል አቋም አለው]። ሰውዬው ትግሬ እንደመሆኑ የፈለገውን ማለት ይችላል “የአማራ ብልፅግና” ባለስልጣናት ግን እንደወትሮው ለስልጣናቸው ብለው በእርስቶቻችንን ላይ ይደራደራሉ ብዬ አላስብም። ካደረጉት ግን ትህነግ ሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት ፈፅማ መጥፊያዋን ራሷ እንደመረጠችው ብአዴናውያንም መቀበርያ ጉድጓዳቸውን በራሳቸው ጊዜ እንደቆፈሩት ይቆጠራል። ጠላት ከሩቅ አይመጣምና ነቅቶ መጠበቅ ነው እንግዲህ!!
     
     
    ሁሉም ነገር በህ አግባብ ነው የሚሆነው ህግ ያስከበርን ህግ መጣስ አይገባም አይ ካልክ ለቀጣይ ተረኛ ትሆናለህ ተዘጋጅ
    Teshome Wolelaw
    ትግሉ መጀመሪያ እንጅ መጨረሻ አይደለም። ገና ብዙ የቤት ስራዎች አሉብን።በተለይ የአማራ ፖለቲከኞች ከመቸውም ጊዜ በተለዬ መንገድ ህዝቡን አንድ አድርጎ በመምራት ትግሉን ዴር ማድረስና ተቋማዊ ማድረግ ይጠበቅባችኋል።
     
    That’s why The war was definitely not for law enforcement.
    • የደም ምድር የነበሩት ወልቃይት፣ጠለምት እና ራያ በጀግኖቻችን ክቡር የህይወት መስዋዕትነት የተገኘው አንፀባራቂ ድል በፖለቲካ ድል ካልታጀበ ታጥቦ ጭቃ ነው።ስለዚህ ገብርዬ ይህ ታላቅ ተጋድሎ ጠያቂ ነውና በዚህ ዙሪያ እንደ አብን ከባዱን ኃላፊነት ለመወጣት ወገብን አጥብቆ በብልህነት መታገል ከፊት ለፊት የሚጠብቀን ታላቁ ስራ ነው።
      አወ ክርስቲ በደማችን የተመለሠዉን እርስታችንን ለማንም ባንዳ ከዚህ በኋላ መፈንጫ አይሆንም ያላችሁን እናንተ ናችሁ ህዝቡ ጠንካራ አቋም እንዲይዝ አድርጉ አስተባብሩ የተለቀቁት እርስቶቻችን በሙሉ አማራዊ ቅርፅ እንዲኖረዉ የምታደርጉትን ሁሉ በጅጉ አጠናክራችሁ ቀጥሉ ከጎናችሁ ነን።
      •  
       
      መዋቅራዊ አሰራሮች አስተዳደራዊ ተግባራት እንዲከናወኑ ይሰራ፤ ይህ ቅርብ የሆናችሁ ሰዎች ቶሎ አከናውኑ። የተከበሩ አቶ ክርስቲያን ታደለ ይህን አጥብቀው ይስሩበት ከክልሉ የብልጽግና ፓርቲ ከአስመላሽ ኮሚቴው ጋር በመተባበር ይሰራ፤ መልካም ጊዜ ይሁንልን!!!!
      •  
    •  
      ከፍተኛ ትኩረት የሚፈልግ ጉዳይ ነው ነገሮች እንዲህ ቀላል የሚሆኑ አይመስለኝም ከፍተኛ ስራ ይጠይቃል ያለቀ ጉዳይ አታስመስሉት ብልጽግናዎች ጦርነቱ ካለቀ በዃላ የአማራን ልጅ ማግደው የሚፈልጉትን ካገኙ በኋላ የሚኖራቸው አቋም ይገመታል እና ጉዳዩን አታቅሉት
      አብን ፣ “የአማራ ክልል መንግሥት” ፣ የወልቃይ አስመላሽ ኮሚቴ እና የራያ አስመላሽ ኮሚቴ በዝግ ስብሰባ ይመካከሩ እና የጋራ አቋም ይያዙ።
      ጩኸት ሳይሆን መሬት የወረደ ሥራ ይሰራ።

Check Also

AMHARA FANO in London at Ethiopian Embassy

የዲያስፓራ መንገደኞች የሚያጋጥማቸው መከራ!

በቦሌ አየር ማረፊያ በፍተሻ እና ጥበቃ አካላት ተጓዦች ላይ የሚፈፀም ውንብድና እና ዝርፊያ! ድርጊቱ የተፈፀመው …

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.