Breaking News
Home / Amharic / የአማራ ሀይልና መከላከያ ከወልቃይት እንዲወጡ በአቢይ አህመድ ትእዛዝ ተሰጠ።

የአማራ ሀይልና መከላከያ ከወልቃይት እንዲወጡ በአቢይ አህመድ ትእዛዝ ተሰጠ።

——————–#ወልቃይትን__እናድን—-———–

የኦህዴዱ አብይ አህመድ ክህደት በወልቃይት ላይ #ግርማካሳ

በርካታ ሜዲያዎች እየዘገቡት ነው፡፡ የአማራ ክልልና የአማራ ልዩ ኃይል፣ የአማራ ሚሊሺያዎችና ፋኖዎች ከወልቃይት ጠገዴ እንዲለቁ ታዘዋል፡፡ በአብይ አህመድ፡፡ እንኩቶ የአማራ ክልልና የጎንደር ዞን የብልጽግና ሃላፊዎች የአብይ አህመድ ትእዛዝ እያፈጸሙ መሆናቸው

ምን ሊሆን ይችላል ብላችሁ ብትጠይቁኝ፣ ህዝብ ታግሎና ተቃውሞ የአብይን አካሄድ ማስቆም ካልቻለ፣ ወያኔዎች በወልቃይት ዉጊያ ይከፍታሉ፣ የአብይ ጦር ከነ ኮረም፣ አላማጣ፣ ቆቦ ለቆ እንደወጣ ከወልቃይትም ለቆ ይወጣና ወያኔ ቦታውን ያለ ዉጊያ እንድትይዝ ያደርጋል፡፡

ታስታውሳላችሁ፣ በኮረም የአማራ ልዩ ኃይል መሽጎ ይጠበቅ ነበር፡፡ መከላከያ እኛ እንጠብቃለን፣ እናንተ ሄዱ ተብለው ምሽጋቸውን እንዲለቁ ተደረገ፡፡ ከዚያ የአማራ ልዩ ኃይል እንዲሌለ ሲታወቅ፣ ምሽጎቹን ጥለው ሄዱ ወያኔ እንደ ፈረሰ እየገሰገሰች ኮረምን ያዘች፡፡ ልክ የያኔው አይነት አሻጥር ነው የአብይ አህመድ መግስት አሁን በወልቃይት ለመስራት እየሞከረ ያለው፡፡

እዚህ ጋር ልብ በሉ ወገኖች፣ አብይ በዚህ አይነቱ የለመደው አሻጥር ወያኔ ወልቃይትን እንድትቆጣጠር ቢያደርግ፣ ሰላም አይመጣም፡፡ ወልቃይት የጦርነት ቀጠና ነው የምትሆነው፡፡ አብይ አህመድ ያንን ነው የሚፈልገው፡፡ በትግሬውና በአማራው መካከል ሰላም እንዲኖር አይፈልግም፡፡

መሆን ያለበት የትግራይ ማህበረሰብ በወልቃይት ጉዳይ ላይ ከአማራው ማህበረሰብ ጋር መነጋገርና መወያየት ነው ያለበት፡፡ ከአማራው ጋር በሚደረግ ስምምነት ነው በወልቃይት ዘላቂ መፍትሄ የሚመጣው፡፡ አሁን አብይ አህመድ በአሻጥር ቢሰጣቸውም፣ በነጋታው መልሰው ሊያጡት ይችላሉ፡፡ ያጡታልም፡፡ በወልቃይት ጒዳይ ትግሬውን፣ አማራዉን አሸናፊ ያደረገ መፍትሄ ማምጣት ይቻላል፡፡ ከባድ አይደለም፡፡

በርካታ የወልቃይት ወገኖች፣ ጎንደሬዎች አብይ አህመድ አምነውት ነበር የሚደገፉት፡፡ በአማራ ክልል የት ነው የብልጽግና ፓርቲ በአንጻራዊነት ድጋፍ የነበረውና ያለው ብለን ብንጠይቅ፣ በዋናነት በጎንደር ክፍለ ሃገር ነው፡፡ምክንያቱም አንድ ነው፡፡ ወልቃይት፡፡ በብልጽግና ፓርቲ ወልቃይትን አግኝተናል በሚል፡፡

አብይ አህመድ አብረዉት ውእደ ስልጣን ያመጡትን ፣ ሃብል አንገታቸው ላየያደረገ፣ እያሞካሻ፣ እያወደሰ ሲከባቸው የነበሩትን ጓደኞቹን እነ አቶ ለማ መገርሳን የካደ ሰው፡፡ “እንዋሃድና አንድ ፓርቲ ስንሆን፣ ህገ መንግስቱን እናሻሽላለን፣ ዘር ከፖለኢትካ እናወጣለን፣ ሪፎርም እናደርጋለን .” ብሎ ፣ አዴፓ የሚለው ድርጅታቸውንና መድረካቸውን እንዲያከስሙ ካደረጋቸው በኋላ፣ በብልጽግ ና ጉብዬ አሸቀንጥሮ ጣላቸው፡፡ ካዳቸው፡፡ ሰዉዮው በክህደትና በዉሸት የተካነ ነው፡፡

ለረጅም ጊዚ በቃላት እየደለለ በጎንደር የብዙ ወገኖች ልብን ሰልቦ ነው የቆየው፡፡ አሁን ደግሞ በይፋ፣ በሚስጥር ከሕወሃት ጋር ተስማምቶወልቃይትን ጨምሮ የጎንደር ሕዝብ ላይ ትል፤ቅ ክህደት እየፈጸመ ነው፡፡

ደግሜ የጎድነር ሕዝብ በኦህዴድ ብልጽግ ና ላይ መጨከን መጀመር አለበት፡፡ ኦህዴድ ብልጽግና ከሕወሃት ቢብስ እንጂ በጭራሽ የተሻለ አይደለም፡፡ ህዝብ ይሂን ተረኛና ዘረኛ ቡድን አምሮ መታገል መጀመ አለበት፡፡

ወልቃይት ላይ የመጨረሻውን ተጋድሎ ተጀምሯል። አሁን በዚህ ሠአት የከባድ መሣሪያ ሩምታ ከተከዜ ማዶ ሆነው እያሠሙ ነው።
ማንኛውም የአማራ #ልዩ_ሀይል_ሆነ_የአማራ__ፋኖ ምሽጉን መልቀቅ የለበትም። ወልቃይትን ሥታነሣ * #ኮ/ል___ደመቀ ዘውዱን እዳትረሣ።#ደመቀ_ያለበትን_ከቅርብ ሠወች ውጭ ማንም ማወቅ የለበትም።#ጦርነቱ #ደመቀን__ለማሥወገድ ጭምር ታርጌት ያረገ ነው።
አብይ ዛሬ ወልቃይት ገብቶ ሢመክር ውሏል። የመከሩባትን ለመጠንቀቅ ያክል ላካፍላችሁ #ልዩሀይሉም__ሆነ___ፋኖ እንዳይገባ ወደ ውጊያ ከገባ ልክ እንደወሎ #አፈግፍግ እያሉ ወልቃይትን ህውሀት ከያዘ በኋላ #የድርድራቸው_ሠነድ ይፋ ሊደረግ እንዳለ ሠምቻለሁ።

Check Also

ከጎጃም አማራ ፋኖ የተሰጠ መግለጫ – ዘመነ ካሴ – Amhara FANO Gojjam

የትግራይ ምሁር የወያኔና የአቢይ አህመድን ሴራ አጋለጠ።

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.