Breaking News
Home / Amharic / ኮሮና ቫይረስ በኢትዮጵያ

ኮሮና ቫይረስ በኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ 2 ሰዎች በለይቶ ማቆያ ክፍል ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል!

የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኮሮና ቫይረስ ተመሳሳይ ምልክት የታየባቸው ሁለት ሰዎች በለይቶ ማቆያ ክፍል ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን አስታውቋል።

ለ910 ሰዎች የጤና ክትትል እየተደረገ ነው ያለው ኢንስቲትዩቱ፥ ስምንት አዳዲስ ጭምጭምታዎች ደርሰውት በኢንስቲትዩቱ የድንገተኛ ህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ምላሽ ማጣራት ተደርጓልም ብሏል።

ከእነዚህ ውስጥ ሁለቱ ከኮሮና ቫይረስ ጋር ተመሳሳይነት ያለው ምልክት በማሳየታቸው በለይቶ ማቆያ ክፍል ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ነው የገለጸው።

አሁን ላይ ቫይረሱ ወደ ሃገር ውስጥ እንዳይገባ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎችን ጨምሮ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑንም በመግለጫው አመላክቷል።

(FBC)
የካቲት 28/2012 ዓ.ም
—————————————————
ክቡራን ቤተሰቦች ሀሳብ አስተያየታችሁን የዜና የመረጃ ጥቆማችሁን ከሰር ባለው ሊንክ አድርሱኝ:: አመሰግናለሁ
አቤል ብርሀኑ (የወይኗ ልጅ)
👉@abel21bot

Check Also

በአሜሪካን ሀገር የምትኖሩ የአማራ ማህበራትና የአማራ ልጆች የት ነው ያላችሁት?? Share!

ድሮን ሲያስተኩስ የነበረው ባንዳ በፋኖ ተያዘ ! እኔን ያየህ ተቀጣ !

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.