Breaking News
Home / Amharic / አፓርታይድ እስከመቼ??

አፓርታይድ እስከመቼ??

(አብርሃ በላይ፣ ኢትዮሚድያ)

የኢትዮጵያ አፓርታይድ ከደቡብ አፍሪቃው አፓርታይድ እጅግ አስፈሪና አገር አፍራሽ፣ ህዝብ አጫራሽ የፖለቲካ ካንሰር ነው። የደቡብ አፍሪቃው አፓርታይድ ከ95% በላይ የሆነውን ጥቁር ህዝብ ህብረቱን አጠናክሮ አንድ ላይ እንዲቆምና አናሳው የነጮች (3%) አገዛዝ እንዲወገድ ረድቷል።

የኢትዮጵያው ግን በነጭና በጥቁር ህዝብ የምንለው አይደለም። የእርስ በርስ እልቂትን የሚጋብዝ በታኝ አፓርታይድ ነው። እየሆነ ያለውም ይኸው ነው።

አሁን ጊዜው የዶ/ር አብይ መንግስት ነው። ይህ መንግስት ዘወትር እንደሚምለው ለኢትዮጵያ ትንሳኤ የቆመ ከሆነ፣ 1) አደገኛውን አፓርታይድ በአዋጅ ያስወግድ 2) ለኢትዮጵያ አንድነት የቆሙ ኃይሎችን ማዋከብ፤ በተለይ የባልደራስ እና የአብን አመራርና አባላትን ማሰር፣ ማሳደድ ያቁም፤ የታሰሩትም ይፍታ! 3) የአፓርታይድ ተጠቃሚዎች እና ጠበቆች የሆኑት የኦዴፓ እና የትህነግ ድርጅት መሪዎችና ካድሬዎቻቸው በእነ መምህር ታዬ ቦጋለ አይነት ታላላቅ የታሪክ ምሁራንና የሀገር አንድነት ጠበቆች በቂ ትምህርት እንዲያገኙ በየደረጃው የሚሰጡ ብሄራዊ ሴሚናሮችን ያዘጋጅ። የኢትዮጵያ ህዝብም ለዚህ ለተቀደሰ ዓላማ የመንግስት ደጀን ሆኖ እንደሚቆም አያጠራጥርም።

ይህን ሳያደርጉ፣ “ኢትዮጵያ አትፈርስም” እያሉ በባዶ ሜዳ መጮህ የሚሰጠው ትርጉም ቢኖር – “የማይነገረው ፕሮጀክታችን እስክንተገብር ድረስ፣ እባካችሁ ትንሽ ታገሱን!” ከማለት ውጪ ሌላ ሊሆን አይችልም።

Check Also

በአሜሪካን ሀገር የምትኖሩ የአማራ ማህበራትና የአማራ ልጆች የት ነው ያላችሁት?? Share!

ድሮን ሲያስተኩስ የነበረው ባንዳ በፋኖ ተያዘ ! እኔን ያየህ ተቀጣ !

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.