Breaking News
Home / Amharic / አማራ ይህን የተደገሰልህን ጉድ ስማ!! share.

አማራ ይህን የተደገሰልህን ጉድ ስማ!! share.

Check Also

AMHARA FANO in London at Ethiopian Embassy

የዲያስፓራ መንገደኞች የሚያጋጥማቸው መከራ!

በቦሌ አየር ማረፊያ በፍተሻ እና ጥበቃ አካላት ተጓዦች ላይ የሚፈፀም ውንብድና እና ዝርፊያ! ድርጊቱ የተፈፀመው …

One comment

  1. (ነጋሳ አብዲሳ)
    የአማራ ክልል ልዩ ሀይል አባላት በሌሎች ብሔረሰብ ባልደረቦቻቸው የተሰጠ ምስክርነት፤
    ————————
    ነፍስ ካወቅኩበት ቀን ጀምሮ ስሰማ ያደግኩት አማራ ስለሚባል አደገኛ ሰው ነው፣ በቃ አማራ የወገኖቸን ጡት እንደ ቆረጠ ለመረዳት ከሚነገረው በላይ በተወለድኩበት አካባቢ ለማስታወሻ የቆመውን ሀውልት ስለምመለከት ውስጤን ያመኛል፡፡
    ይሁንና ዶክተር አብይ ወደ ስልጣን ሊመጣ አካባቢ ጀምሮ ሌላም ጠላት እንዳለን ተረዳሁ እሱም ትህነግ (ወያኔ) የሚባል ነበር፡፡ ይህ ቡድን አማራ ከሚባለው በላይ የኦሮሞ ጠላት መሆኑን ነጋሪ ሳያስፈልገኝ ተረድቻለሁ፤ ይሁንና ላለፉት ሰባት አመታቶች በሀገር በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ እየሰራሁ ስለምገኝ እንደፈለግኩ እንኳ ተሳድቤ መናገር አልቻልኩም ነበር፡፡ ምክንያቱ ደግሞ አብረውኝ የተሰለፉ የትግራይ ተወላጆች ስላሉ ማስከፋት እንዳይሆንብኝ ብየ ነው፤(እንዲህ ከድተው ወንድሞቸን ሊያሳርዱ ምነው ልክ ልካቸውን በነገርኳቸው) ብየም አስባለሁ፡፡
    ይሁንና ለዛሬ ልናገር የምፈልገው አማራ የሚባለው ህዝብ የወለዳቸው ልጆች ወይም የአማራ ክልል ልዩ ሀይል ስለሚባሉትና ይህንን ተደግፌ በውስጤ ስለተፈጠረው አዲስ ነገርና ፀፀት ነው፡፡
    ራያ ላይ የጠላትን ጦር ለማጥቃት የቀረን ጀምሩ የሚል ትዕዛዝ ነበር፤ እሱም አልቀረምና ትዕዛዝ ተሰጠን፤ በርካታ ተጋድሎዎችን ፈፀምን፣ በርካታ የጠላት ጦር ደመሰስን፤ ከኛም የተወሰኑ ጓደኞቻችን ተጎድተዋል፡፡
    በዚህ ሁሉ የአማራ ልዩ ሀይሎች አብረውን ነበሩ፤ እጅግ በሚገርም ሁኔታ ውስጣቸው እሳት ያለ ይመስለኛል፤ አረ እንዴውም ይነዳል መሰለኝ፤ ፈፅሞ ወደ ኋላ አያዩም፤ እኛን ቆይ ቦታውን በደንብ አታውቁትም እንጥረግላችሁ ይሉናል፤ አልፈው ይሄዳሉ ስንጠጋ እጅግ ብዙ የትግራይ ልዩ ሀይል ተደምስሶና ተማርኮ እናገኛለን፡፡
    በዚህ ሁሉ አንድ ከበድ ያለ ውጊያ ገጠመን እልህ አስጨራሽ ነበር፤ የጠላት ጦር የመሸገበትን ጥሶ መግባት ከበደን፤ ብዙ ጓዶቻችን ተጎዱ ኋላ ላይ ደመስስናቸው፤ እልህ ውስጥ ነበርን፤በመሀል አንድ በእድሜ ከ 18 እስከ 20 አመት የምትሆን የጠላት አባል ተጎድታ እያለ ተኮሰችብን፤ መሳሪያየን አዙሬ ልተኩስ ስል ተው አሉኝ፤ እንዴት ስል ተው አትግደላት አሉኝ፤ እናም ለብዙ ደቂቃ ለምነው አሳመኗትና እጅ እንድትሰጥ አደረጓት፤ እጅግ የገረመኝ እህታቸውን ያገኙ ነው የመሰላቸው፤ እንባ ከአይናቸው ሲመነጭ እመለከታለሑ፡፡
    እርግጠኛ ሆኘ የምነግራችሁ እርሷ ጊዜ ብታገኝ አሁንም ትተኩስብናለች፤ ሳያት እልህ እንጅ ሀዘን እየተሰማት አይደለም፤ አለመቻል አሸነፋት እንጅ፡፡ እነርሱ ግን ወንድሞቻቸው ተጎድተው እንኳ ለእርሷ ያዝናሉ፡፡
    ይገርማል እነዚህ ልዩ ሀይሎች የወጡት ከአማራ ህዝብ ነው፤ ካላችሁ ያ ህዝብ ፈፅሞ የኔን አያቶች ጡት ቆርጧል ብየ ለማመን ይከብደኛል፡፡ የማረክናት ልጅ አጋሮች ግን የላኳት ሰዎች በወንድሞቸ ላይ የፈፀሙትን በማየት ብቻ እንደሚያደርጉት ማመን ይቻላል፡፡
    ይገርማል የአማራን ልዩ ሀይል አለማመስገን አይቻልም፤ እነርሱ ባይኖሩ ምናልባት ከዚህ የከበደ መስዋዕትነት ልንከፍል እንችል ነበር እነርሱ ጀግኖች ናቸው፤ክብር ይገባቸውል፡፡
    (ምክትል አስር አለቃ ነጋሳ አብዲሳ፤ ከደቡብ እዝ)
    #ሸር_በማድረግ_የወያኔን_ተንኮል_አለም_እንዲረዳው_እናድርግ!
    ክብር ለጀግናው መከላከያችን፣

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.