Breaking News
Home / Amharic / በደቡብ ጎንደር ዞን ታስረው የነበሩት የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አመራሮች በብር ዋስትና ከእስር ተፈተዋል

በደቡብ ጎንደር ዞን ታስረው የነበሩት የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አመራሮች በብር ዋስትና ከእስር ተፈተዋል

***
ሰኔ 15 ቀን 2012 ዓ.ም የደቡብ ጎንደር ዞን አመራሮች ላይ የግድያ ወንጀል ለመፈፀም አስባችሁ ነበር በሚል በፖሊስ ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት የንቅናቄያችን የደቡብ ጎንደር ዞን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ም/ሰብሳቢ አቶ ቢሰጥ አሰፋ እና የደርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ጌታቸው አዱኛ ጥቅምት 10 ቀን 2012 ዓ.ም በደብረ ታቦር ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር፡፡

በዕለቱ በዋለው ችሎትም ፓሊስ አሉኝ ያላቸውን ምስክሮችና የተጠርጣሪዎችን የስልክ ልውውጥ ከኢትዮ ቴሌኮም ያላቀረበ ሲሆን ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠውም ጠይቋል። ተጠርጣሪዎች በበኩላቸው ፓሊስ በተሰጠው ጊዜ አለኝ የሚለውን ማስረጃ አለማቅረቡን ገልፀው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ሊሰጠው አይገባም ሲሉ ተቃውመዋል።

የግራ ቀኙን ክርክር ያዳመጠው የደብረታቦር ወረዳ ፍርድ ቤት የፓሊስን የተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ጥያቄ ውድቅ በማድረግ ተጠርጣሪዎቹ በ5ሺህ ብር ዋስ እንዲፈቱ ውሳኔ የሰጠ ሲሆን ተጠርጣሪዎቹም ዛሬ ከእስር ተፈተዋል።

አንድ አማራ ለሁሉም አማራ፤ ሁሉም አማራ ለአንድ አማራ!

Check Also

በአሜሪካን ሀገር የምትኖሩ የአማራ ማህበራትና የአማራ ልጆች የት ነው ያላችሁት?? Share!

ድሮን ሲያስተኩስ የነበረው ባንዳ በፋኖ ተያዘ ! እኔን ያየህ ተቀጣ !

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.