Breaking News
Home / Amharic / የአማራ ባንክ ምስረታና ምዝገባ !

የአማራ ባንክ ምስረታና ምዝገባ !

File Edit View Insert Format Tools Table Paragraph  

የአማራ ባንክ ውክልናን በተመለከተ አጭር ማብራሪያ ፤

1. ማን ነው የሚወከል ?
ከኮቪድ አንፃር እና የባንኩ ባለአክሲዮኖች ቁጥር ከ150,000 በላይ በመሆናቸው በባለ አክሲዮኖች እንዲወከሉ የሚፈለገው የባንኩ አደራጆች ናቸው ።
ነገር ግን ተመራጭ አማራጭ ባይሆኑም ባለአክሲዮኖች የሚከተሉት ሁለት መብቶች አሏቸው ። አንደኛ ከአደራጆች ውጭ ያለ ሌላ ማንኛውም ሰው የመወከል መብት አላቸው ። ሁለተኛ ማንንም ሰው አልወክልም እኔ በቀጥታ ነው ስብሰባ የምሳተፈው ካሉም መብታቸው ነው ።
ነገር ግን እነዚህን ሁለት አማራጮች በስፋት ጥቅም ላይ ከዋሉ በስብሰባው የሚገኘውን ሰው ቁጥር ያበዛብናል ። ይህ ሲሆን ደግሞ በኮቪድ እና ሎጂስቲክ ጉዳዮች ስብሰባው ማካሄድ ያስቸግረናል ። በዚህም የባንኩ ምስረታ ይጓተታል ። ስለዚህ ባለአክሲዮኖች ከላይ የተጠቀሱት ሁለት መብቶች ቢኖራቸውም የባንኩን ምስረታ ለማፍጠን ሲባል አደራጆችን እንድትወክሉና እና ምስረታውን እንድናፈጥነው ስንል በአክብሮት እንጠይቃለን ።
ይህን ስንል ግን ባንኩ በአደራጆች ጉባኤ ብቻ ይመሰረታል ማለት አይደለም ። ሌላ ሰው በሚወክሉ ባለአክሲዮኖች ፤ በቀጥታ መገኘት በሚፈልጉ ባለአክሲዮኖች ፤ ከፍተኛ ድርሻ ባላቸው ባለአክሲኖች ፤ ብዙ ህዝብ በሚወክሉ ድርጅቶች ፤ ማህበራት ፤ እድሮች ወዘተ የሚካሄድ ይሆናል ። አደራጆችን ወክሉ ስንል የተሳታፊውን ቁጥር ለመቀነስ እንጂ አደራጆች ብቻ ስብሰባውን ያካሂዱታል ብላችሁ ያልተገባ ግንዛቤ እንዳትይዙ ለማሳሰብ እንወዳለን ።
የባንኩ አደራጆች በቁጥር 34 ናቸው ። የአደራጆቹ ኘሮፋይል ውልክና በምትሰጡበት ጣቢያ በፖስተር የሚተዋወቅ ይሆናል ። ከእነዚህ አደራጆች ውስጥ ይወክለኛል የምትሉትን አንዱን አደራጅ ወክሉት ።
የተጠናል ወይም የቡድን ውክልና መስጠት ይቻላል ። የተናጠል ውክልና ማለት አንድ ባለአክሲዮን አንድ አደራጅ ሲወክል ነው ። የቡድን ውክልና ማለት ደግሞ ለምሳሌ አንድ አስር ባለአክሲዮኖች ሰብሰብ ብለው በአንድ የውክልና ፎርም አንድ አደራጅ እንዲወክል ሲያደርጉ ነው ። ወጭ ከመቀነስ አንፃር እኛ የምንመርጠው የቡድን ውክልናን ነው ።
በውክልናው ለአደራጁ የምትሰጡት መብት ሁለት ነው ። አንደኛው በጠቅላላ ጉባኤ ላይ ተገኝቶ ውሳኔዎችን የማስተላለፍ ነው ። ሁለተኛ የባንኩን መመስረቻ ፅሁፍና መተዳደሪያ ደንብ እንዲፈርም ናቸው ።
2. ውክልና የሚሰጠው መቸና የት ነው ?
ከህዳር 1-15 ፤ 2013
በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ እና ድሬዳዋ የምትገኙ ባለአክሲዮኖች የምትወክሉት በየአካባቢያችሁ የሚገኝ የፌደራሉ ውልና ማስረጃ ፅ/ቤት እየቀረባችሁ ነው ። አዲስ አበባ ላይ በየክፍለ ከተማው ባለ የፌደራሉ ውልና ማስረጃ ፅ/ቤት ለአማራ ባንክ ብቻ የተመደበ መስኮት ስላለ እየቀረባችሁ ውክልና መስጠት ትችላላችሁ ።
ከህዳር 16-30 ፤ 2013
በአማራ ክልል የዞን ከተሞች ያላችሁ ባለአክሲዮኖች የምትወክሉት በምናመቻቸው የፌደራሉ ውልና ማስረጃ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ይሆናል ። ይህንን ወደፊት የምነግራችሁ ይሆናል ።
ከህዳር 1-30 ፤ 2013
በአማራ ክልል የወረዳ ከተሞች እና በሌሎች ክልሎች ያላችሁ ባለአክሲዮኖች የምትወክሉት በየአካባቢያችሁ የሚገኙ የወረዳ የውልና ማስረጃ አገልግሎት የሚሰጡ የፍትህ ተቋማት ነው ። ውክልናውን ከሰጣችሁ በኋላ በተራ ቁጥር 3 ከታች ከተጠቀሱ ዶክመንቶች ጋር በአማራ ባንክ የአዲስ አበባ የፖስታ ሳጥን ቁጥር 149 አድራሻ መላክ አለባችሁ ።
በውጭ አገር የምትኖሩ ዳያስፖራ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የምትወክሉት ደግሞ በምትኖሩበት አገር ኤምባሲ በመቅረብ ይሆናል ። እናንተም ከላይ የተጠቀሱ ሙሉ ዶክመንቶችን በአማራ ባንክ ፖስታ ሳጥን መላክ አለባችሁ ።
3. ውክልናውን ለመስጠት የሚያስፈልግ ዶክመንት ፤
ለመወከል ስትመጡ የሚከተሉትን ዶክመንቶችን መያዝ አለባችሁ
የታደሰ መታወቂያ ፤ የቀበሌ ፤ መንጃ ፈቃድ ፤ ፓስፖርት ወዘተ እንደ መታወቂያነት ያገለግላል ።
አክሲዮን ስትገዙ የሞላችሁት የአማራ ባንክ ፎርም እና ገንዘቡን ገቢ ያደረጋችሁበት የባንክ ደረሰኝ ።
ለህፃናት አክሲዮን ከገዛችሁ የልደት ሰርተፊኬታቸው ያስፈልጋል።
 
አማራ ባንክ አ.ማ አደራጆች::
 
To invest in Amhara Bank send e-mail to: amhara1@amharaonline.org
 
 

Check Also

በአሜሪካን ሀገር የምትኖሩ የአማራ ማህበራትና የአማራ ልጆች የት ነው ያላችሁት?? Share!

ድሮን ሲያስተኩስ የነበረው ባንዳ በፋኖ ተያዘ ! እኔን ያየህ ተቀጣ !

News in Pictures

Time in Ethiopia

Multi threaded Redundant Dedicated Server in USA and in Europe.